4.9 C
London
Wednesday, February 5, 2025

የታላቁ የህዳሴ ግድብ ቀሪ ግንባታ አዲስ የ፹ ቢሊዮን ብር ወጪ ያስፈልገዋል

በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በዋጡት የቦንድ ግዢ እየተገነባ ያለው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቀሪ ስራዎችን ለማከናወን ተጨማሪ ሰማኒያ ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ተገለጸ። ይህ መጠን የግድቡ ግንባታ በተጀመረበት ወቅት ለመጀመሪያ ግምት ከተያዘው በጀት ጋር እኩል መሆኑ ግራ መጋባትን ፈጥሯል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት እንዳስታወቀው፣ የግድቡ ግንባታ አሁን ከዘጠና ሰባት ነጥብ ስድስት በመቶ በላይ ደርሷል። ነገር ግን ቀሪውን ሁለት ነጥብ አራት በመቶ ስራ ለማጠናቀቅ የሚያስፈልገው ወጪ በርካታ መሆኑ ከፍተኛ ትኩረትን ስቧል።

እስካሁን ድረስ ከህዝብ የተሰበሰበው ገንዘብ ሃያ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ የዳያስፖራው ድርሻ አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ብቻ መሆኑ ተገልጿል። ይህንን ተሳትፎ ለማሳደግ በተለያዩ የክፍያ መተግበሪያዎች አማካኝነት መዋጮ መክፈል እንደሚቻል የፕሮጀክቱ ሥራ አስፈጻሚ ዳይሬክተር ደክተር አረጋዊ በርሄ አስታውቀዋል።

Latest news
Related news